BBC News, አማርኛ - ዜና
እንዳያመልጥዎ
ኤርትራ ህወሓት ለዳግም ጦርነት እየተዘጋጀ ነው አለች
የኤርትራ መንግሥት ህወሓት ለዳግም ጦርነት በዝግጅት ላይ እንደሆነ በመግለጽ እራሱን ለመከላከል አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ። የኤርትራ መንግሥት በማስታወቂያ ሚኒስቴሩ በኩል ዛሬ ግንቦት 09/2104 ዓ.ም. ባሰፈረው መልዕክት ህወሓት በኤርትራ ድንበር በኩል እና በምዕራብ ትግራይ አቅጣጫ በሁለት ግንባሮች ጦርነት ለመክፈት እየተዘጋጀ ነው ብሏል።
በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያ ጋር ምን ዓይነት ግንኙነት ሊኖራቸው ይችላል?
የ30 ዓመታት የእርስ በእርስ ጦርነት ያሽመደመዳት ሶማሊያ በበርካታ ውስጣዊና ውጫዊ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የተወጠረች አገር ናት። በዚያ ላይ ስር የሰደደ ሙስና እንዲሁም የጎሳ ክፍፍል ይንጣታል። አክራሪው ታጣቂ ቡድን አል-ሸባብ ሶማሊያን ከጥግ ጥግ ከማናጋት አልፎ የአፍሪካ ቀንድ ስጋት ከሆነም ሰነባብቷል። ለመሆኑ የሐሰን ሼክ ሞሐሙድ መመረጥ ለሶማሊያ፣ ለአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ምን ማለት ነው? በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነትስ ሊለወጥ ይችላል?
ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ያሉበትን ማወቅ እንዳልቻሉ ባለቤታቸው ተናገሩ
ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ አዲስ አበባ ውስጥ ከቤታቸው እንደወጡ አለመመለሳቸውን ባለቤታቸው ወ/ሮ መነን ኃይሌ ለቢቢሲ ገለፁ።
የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንችላለን? ሁሉንም እሳት በውሃ ማጥፋትስ ይቻላል?
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል። በዚህም የሰዎች ሕይወት አልፏል፤ በንብረት ላይም ከፍተኛ ውድመት ደርሷል።ባለፉት 9 ወራት ብቻ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ በደረሰ የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ውድመት መድረሱ ተገለጸ።
አሜሪካ፣ ሰሜን ኮሪያዊ የኮምፒውተር ሊቆች የጎን ውጋት ሆኑብኝ አለች
ማንነታቸውን ደብቀው በአሜሪካ የበይነ መረብ ገበያ ሥራ አመልክተው የሚቀጠሩ የኮምፒወተር ቴክኖሎጂ ብልሆች ለደኅንነቴ ሥጋት ሆነዋል አለች።
በአማራ ክልል ከዛሬ ጀምሮ የጦር መሳሪያ ምዘገባ ሊካሄድ ነው
በአማራ ክልል ከማክሰኞ ጀምሮ በግለሰቦች እጅ የሚገኝ የጦር መሳሪያ ምዝገባ ሊካሄድ መሆኑን የክልሉ የሰላምና የፀጥታ ቢሮ አስታወቀ። የጦር መሳሪያ ምዝገባው ከነገ ከማክሰኞ ግንቦት 09/2014 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ አርብ ድረስ ለአራት ተከታታይ ቀናት እንደሚካሄድ የቢሮው ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።
ከመጋረጃ ጀርባ የሚካሄደው የሩሲያና የምዕራባውያን ሰላዮች ጦርነት
ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት ወዲህ በአሁኑ ወቅት ሩሲያና ምዕራባውያን በስለላው መስክ ትግል ላይ ናቸው። ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወረራ ከመክፈቷ ከዓመታት ቀደም ብሎ በተቀናቃኞቿ ግዛት ውስጥ ሰፊ የስለላ መረብ ዘርግታ መረጃ ስትሰበስብ እንዲሁም እርምጃ ስትወስድ እንደቆየች ይነገራል። አሁን ሁለቱ ወገኖች በስለላው መስክ ለይቶላቸው ተፋጠዋል።
የክርስቲያን መሪዎች በፍልስጤማዊቷ ጋዜጠኛ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ የደረሰውን ጥቃት አወገዙ
በእየሩሳሌም የሚገኘው የቫቲካን ተወካይ እስራኤል የእምነት ነፃነትን ለማስከበር የገባችውን የአስርት አመታት ስምምነት "በአሳዛኝ ሁኔታ እየጣሰች ነው" ሲሉ ከሰዋል።
ማክዶናልድስ ከ30 ዓመታት አገልግሎት በኋላ ከሩሲያ ነቅሎ ወጣ
ማክዶናልድስ የተሰኘው ፈጣን ምግብ አቅራቢ ድርጅት ከ30 ዓመታት በኋላ ከሩሲያ ነቅሎ እየወጣ ነው።
አነጋጋሪ ጉዳይ
በተወሰኑ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በስፋት ስለሚታየው የጉሮሮ ካንሰር ምን እናውቃለን?
ምንም እንኳ እርግጠኛው የጉሮሮ ካንሰር መነሻ ምክንያቶች እነዚህ ናቸው ተብሎ ባይበየኑም፣ በበርካታ አገራት የአልኮል መጠጥን የሚያዘወትሩ፣ በሲጋራ ሱስ የተጠመዱ ሰዎች በጉሮሮ ካንሰር እንደሚጠቁ ጥናቶች ያሳያሉ። በተጨማሪም የሚፋጁ ምግቦች እና መጠጦችን የሚያዘወትሩ ለጉሮሮ ካንሰር የመጋለጥ ዕድላቸው ሰፊ መሆኑን እነዚህ ጥናቶች ጠቁመዋል።
በሶማሊያ ለሁለተኛ ጊዜ ፕሬዝዳንት የሆኑት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ ማን ናቸው?
አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ ሥልጣነ መንበር ሲጨብጡ የመጀመሪያቸው አይደለም። እአአ ከ2012 እስከ 2017 የሶማሊያ ስምንተኛው ፕሬዝዳንት ነበሩ። በ2017 በድጋሚ ሲወዳደሩ ግን የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ረቷቸው።
ዘ ኢኮኖሚስት ዘጋቢው ከኢትዮጵያ መባረሩን ተቃወመ
ዘ ኢኮኖሚስት የተባለው ጋዜጣ የኢትዮጵያ ዘጋቢው ፈቃድ መነጠቁን አወገዘ።
ኢሰመኮ በሰሜን ኢትዮጵያ ውጥረት እየጨመረ መምጣቱ እንዳሳሰበው ገለጸ
በትግራይ ክልልና በፌደራል መንግሥት ኃይሎች መካከል ውጥረት እየጨመረ መምጣቱ እንዲሁም አልፎ አልፎም ግጭቶች ሪፖርት መደረጋቸው እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ።
መንግሥት በኦሮሚያ ባለው ታጣቂ ቡድን ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
የመንግሥት ኃይል በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች በሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ቡድን ላይ የተጠናከረ ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
ፑቲን ፊንላንድ ኔቶን መቀላቀል መፈለጓ 'ስህተት ነው' ሲሉ አስጠነቀቁ
ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት እንድታቆምና ገለልተኛ መሆኗን ማቆሟ ትልቅ ስህተት እንደሚሆን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስጠነቀቁ።
ሕንዳውያኑ ወላጆች የልጅ ልጅ አላሳየንም ያሉትን ልጃቸውን ለምን ከሰሱ?
በሕንድ ወደ ፍርድ ቤት ያመራው ያልተለመደ ክስ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። በዚህም እናትና አባት ብቸኛ ልጃቸውንና ሚስቱን ከስድስት ዓመት ጋብቻ በኋላ የልጅ ልጅ አላሳዩንም ሲሉ በፍድር ቤት ክስ አቅርበዋል።
ሩሲያ ለፊንላንድ የምታቀርበውን የኤሌክትሪክ ኃይል ልታቋርጥ ነው
አርኤኦ ኖርዲክ የተሰኘው የሩሲያ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋም ከክፍያ ጋር በተያያዘ ችግር እንደገጠመው በመግለጽ ለፊንላንድ የሚያቀርበውን ኤሌክትሪክ ከዛሬ ቅዳሜ ጀምሮ አቋርጣለሁ ብሏል።
የሩዋንዳውን የዘር ማጥፋት ወንጀለኛ ፍለጋ በመቃብሩ ውስጥ ተጠናቀቀ
እ.ኤ.አ. በ 1994 በሩዋንዳ በተፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል በጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት የተከሰሰው እና በወንጀሉ ከሚፈለጉ ሰዎች የመጨረሻው ዋና ተፈላጊ ግለሰብ በሽሽት በኖረበት ዚምባብዌ ሕይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።
ስዊዲን እና ፊንላንድ ለምን ኔቶን ለመቀላቀል ፈለጉ? የሩሲያ ምላሽስ ምን ይሆናል?
ፊንላንድ እና ስዊዲን በጦርነት ወቅት ከየትኛውም ወገን ጎን ላለመቆም እና ማንኛውንም ወታደራዊ ጥምረት ያለመቀላቀል ዘመናትን ያስቆጠረ ታሪክ ነበራቸው። ይህ ታሪክ ተቀልብሶ አሁን ኔቶን ለመቀላቀል ከጫፍ ደርሰዋል።
ከየፈርጁ
በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይሆን?
ላለፉት 17 ወራት በጦርነት ሲናጥ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢ የትግራይ ኃይሎች ከአፋር ወጥተናል ማለታቸውን ተከትሎ መረጋጋት ያሳየ ቢመስልም ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ዳግም ግጭቶች ሊያገርሹ እንደሚችሉ እየታዩ ነው። የትግራይ ኃይሎች ከኤርትራ ጋር አዋሳኝ በሆኑት አካባቢዎች ላይ የከባድ መሳሪያ ጥቃት ከፍተው ለአጭር ጊዜ የቆየ ወታደራዊ ግጭት መካሄዱን ቢቢሲ ከምንጮቹ አረጋግጧል።
ያድምጡ, ቢቢሲ አማርኛ ዜና
20:29 EAT - 20:44 EAT
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እንዴት ሊጠናቀቅ ይችላል?
በሊጉ 15 ጨዋታዎች ይቀራሉ። ለዋንጫ ከሚደረገው ፉክክር በተጨማሪ በአውሮፓ ደረጃ የሚወዳደሩ እና ከሊጉ የሚወርዱ ቡድኖች ተለይተው አላለቁም። ሊጉ በምን መልኩ ሊጠናቀቅ ይችላል?
ሕዝቡ የማይመርጥበት የሶማሊያው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ
ሶማሊያ ለረጅም ጊዜ የተጓተተውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዛሬ እሁድ ግንቦት 07/2014 ዓ.ም. ታካሂዳለች። ይህም መጀመሪያ ሊደረግ ከታቀደው ከአንድ ዓመት በላይ ዘግይቶ ነው።
ኬንያዊቷ ነርስ በዓለም አቀፍ ውድድር አሸንፋ 250 ሺህ ዶላር ተሸለመች
ኬንያዊቷ ነርስ የዓለም አቀፉን የነርሶች ሽልማት ውድድርን በማሸነፍ 250 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ተበረከተላት። በሰሜን ኬንያ መርሳቢት በሚገኘው ሆስፒታል የምትሰራው ነርስ ቀበሌ (Qabale) ዱባ ይህን ሽልማት ያሸነፈችው በምትኖርበት ማኅብረሰብ የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ባደረገችው ጥረት ነው።
'በተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖች ከዓለም ዓይን የተሰወረ ጦርነት እየተካሄደ ይገኛል' ኦፌኮ
በተለያዩ የኦሮሚያ ዞኖች ከዓለም ዓይን የተሰወረ ጦርነት እየተካሄደ የሰው ህይወት እየጠፋ ነው ሲል የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ዛሬ ግንንቦት 04/2014 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሰጠው መግለጫ አመለከተ።
በሶማሌ ክልል በባህላዊ የምርጫ ሥነ ሥርዓት ላይ በፀጥታ ኃይሎች የተፈጸመውን ግድያ ኢሰመኮ ኮነነ
በሶማሌ ክልል ቦምባስ ከተማ በባህላዊ ሥነ ሥርዓት የጎሳ መሪ ለመምረጥ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ በፀጥታ ኃይሎችና በታጠቁ ግለሰቦች በተፈጸሙ ጥቃቶች የ11 ሰዎች ህይወት መጥፋቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮነነ።
ተደራራቢው የኢትዮጵያ ሴት ጋዜጠኞች ጭቆና
ቢቢሲ ለዚህ ዘገባ ያነጋገራቸው ሴት ጋዜጠኞች በተለይም የጋዜጠኝነት ሥራ በጀመሩባቸው የመጀመሪያ ግዜያት የተለያዩ ማባበያዎችን በማቅረብ፤ ባስ ሲልም ማስፈራሪያ እና ጉልበት በመጠቀም አካላዊ ጥቃቶች በሥራ ቦታቸው አጋጥሟቸዋል። ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ስር መስደዳቸውን እና የተለመደ የየቀን ሕይወት አካል መሆኑን ሴት ጋዜጠኞቹ ይናገራሉ። እነዚህ ጥቃቶች ኢኮኖሚያዊ መልክን በያዙ ማባበያዎችም ተሸፍነው ብቅ እንደሚሉ ጋዜጠኞቹ ይናገራሉ።
የጉግል መተርጎሚያ በትግርኛና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች አገልግሎት ጀመረ
ግዙፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጉግል ትግርኛና ኦሮምኛን ጨምሮ ከ300 ሚሊዮን በላይ የሚናገራቸውን 24 አዳዲስ ቋንቋዎች በጉግል መተርጎሚያ ዝርዝሩ ውስጥ አካቷቸዋል።በኢትዮጵያ እና በኬንያ ወደ 37 ሚሊዮን የሚጠጉ ነዋሪዎች ኦሮምኛን የሚናገሩ ሲሆን ስምንት ሚሊዮን የሚጠጉ የኤርትራና የትግራይ ተወላጆች ትግርኛን ይናገራሉ።
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ተይዞ ስለቆየበት ሁኔታ በዝርዝር ተናገረ
ከአንድ ሳምንት በላይ ደብዛው ጠፍቶ የነበረው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፤ ከመኖሪያ ቤቱ 'የተደራጀ የሕገ-ወጥ ቡድን' በሚመስል አካል ከተያዘ በኋላ ጦር ኃይሎች አካባቢ ባለ 'የድሮ ቤት' ውስጥ ሳያቆዩኝ አይቀርም አለ።
አጃኢብ!
ቪዲዮ, አባትና ልጅ ከ58 ዓመታት በኋላ በፌስቡክ አማካኝነት ተገናኙ, ርዝመት 3,11
ጁሊ ሉንድ ከ58 ዓመታት በኋላ አባቷን አግኝታለች። ጁሊ አብዛኛውን ዕድሜዋን ያሳለፈችው አባቷን በመፈለግ ነው።
ከጨረቃ በተወሰደ አፈር ለመጀመሪያ ጊዜ ተክሎችን ማብቀል ተቻለ
ሳይንቲስቶች ከጨረቃ በተገኘ አፈር ተክሎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማብቀል ችለዋል።
በአንድ ጀንበር ከእውቅ ባለፀጎች በላይ ባለሃብት የሆነው የሎተሪ እድለኛ
እድለኛው በዩናትድ ኪንግደም ታሪክ 184 ሚሊዮን ፓዎንድ (ከ11 ቢሊየን 799 ብር በላይ ) በሎተሪ እጣ አሸነፈ።
ቪዲዮ, ከአሲድ ጥቃት የተረፉ ሴቶች ከጥቃት በኋላ ፍትሕ ብቻ በቂ አይደለም ይላሉ, ርዝመት 3,20
የአሲድ ጥቃት ሰለባዎች መሰል ጥቃቶችን ለመግታት ጥቃት አድራሾችን ከሕግ ፊት ማቅረቡ በቂ አይደለም ይላሉ።
ሶስት ሴቶችን የገደለው ወንጀለኛ ማረሚያ ቤት ውስጥ ማግባት እንደሚፈልግ ገለጸ
ወንጀለኛው ማርሻ ማኮኔል፣ ኤምሊ ዴላግራንዴ እና ሚሊ ዶውለር የተባሉ ሴቶችን በጭካኔ በመግደል ጥፋተኛ ተብሎ ሁለት የእድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት ነበር።
ሩሲያ ያሰረቻትን የቅርጫት ኳስ ተጫዋች አሜሪካ ባለእስረኛ የመለዋወጥ ፍላጎት እንዳላት ተነገረ
ሩሲያ ጉዳይዋ በፍርድ ቤት እየታየ የምትገኘውን ታዋቂ አሜሪካዊት የቅርጫት ኳስ ተጫዋችን አሜሪካ ውስጥ በሚገኝ እስረኛ ለመለዋወጥ ፍላጎት እንዳላት ተነገረ።
ከኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በኋላ ወደ ሥራ ቦታ መመለስና ፈተናዎቹ
ከሁለት ዓመት በኋላ በርካታ የዓለማችን ድርጅቶች ሠራተኞቻቸው በየቤታቸው ከመስራት ወደ ቢሮ ስለመመለስ እንዲያስቡ እያደረጉ ነው። አብዛኞቹም ወደ ሥራ ቦታቸው መመለስ ጀምረዋል።
በአንዴ ዘጠኝ ሆነው የተወለዱት ልጆች አንደኛ ዓመታቸውን አከበሩ
በዓለም ብቸኛ የሆኑት ዘጠኝ ልጆች አንደኛ ዓመታቸውን እንዳከበሩና መልካም ጤና ላይ እንደሚገኙ አባታቸው ለቢቢሲ ገለጸ።
ከቡና ጋር ተቀላቅሎ የተላከ 500 ኪሎ ግራም ኮኬይን ተያዘ
የስዊዘርላንድ ፖሊስ ቡና አምራች ወደሆነው ኔስፕሬሶ ፋብሪካ ከቡና ጋር ተቀላቅሎ የተላከ 500 ኪሎ ግራም ኮኬይን መያዙን አስታወቀ።
"የወር አበባቸው ሲመጣ አመድ ላይ ይቀመጣሉ"
ከ82 በላይ ሴት ሠራተኞች ያሉት አደይ፣ 100 ጊዜ የሚታጠብ ሞዴስ ነው። ሚካል ማሞ የአደይ መሥራች ናት። አንዲት ሴት በወር ውስጥ ከሦስት እስከ ሰባት ቀናት የምትጠቀመው ሞዴስ እየታጠበ እስከ ሁለት ዓመታት ያገለግላል ትላለች ሚካል። ሚካል ሥራዋ ሞዴስ ማምረት ብቻ አይደለም። የወር አበባ ድህነትን ለመቅረፍ ትታገላለች። ሞዴስ ከቀረጥ ነጻ እንዲሆን፣ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርብ፣ በመላው አገሪቱ ተደራሽ እንዲደረግም ንቅናቄ ከሚያደርጉ አንዷ ናት።
የተመለሱ ጥያቄዎች
ኢትዮጵውያንን እየፈተነ ያለው የኑሮ ውድነት መፍትሄው ምን ይሆን?
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የዋጋ ግሽበት በተከታታይ ጭማሪ ሲያሳይ ቆይቷል። በተለይም ኀብረተሰቡ በዕለት ተዕለት በሚጠቀምባቸው መሰረታዊ ፍጆታዎች፣ በግንባታ እቃዎችና በሌሎች ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ንረት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዜጎችን ህይወት እጅግ እየተፈታተነው ይገኛል። የምጣኔ ባለሙያዎችም እርምጃ ካልተወሰደ መዘዙ ብዙ እንደሆነ አበክረው እየተናገሩ ነው።
የወር አበባ እረፍት ዘግይቶም ቢሆን ተቀባይነት እያገኘ ይሆን?
ሁንም ድረስ እንደ አሜሪካ ባሉ ባደጉት አገራት ጭምር እንኳን ሴቶች ወር አበባቸውን ሲያዩ እረፍት እንዲወጡ አልያም ከቤታቸው እንዲሰሩ የሚያደርጉ ሕጎች እምብዛም አይስተዋሉም።
የሞባይል ኔትዎርክ የመጨረሻው ቴክኖሎጂ 5ጂ ለኢትዮጵያ ምን ይፈይዳል?
አምስተኛው ትውልድ ወይም 5ጂ ዓለም የደረሰበት የመጨረሻው ፈጣን የሞባይል ኔትዎርክ ቴክኖሎጂ ነው። "የመጨረሻው ፈጣን" ማለት 2 ሰዓት የሚፈጅ ፊልምን በሰከንዶች ውስጥ ማውረድ [ዳውን ሎድ] ማድረግ የሚያስችል ነው። ትናንት በኢትዮጵያ ወደ ሥራ የገባው ይህ ቴክኖሎጂ፣ ለቅድመ ገበያ [ለማስተዋወቅ] በአዲስ አበባ በተመረጡ አካባቢዎች ላይ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
አንሶላችንን መቀየር ያለብን በምን ያህል ቀናት ልዩነት መሆን አለበት?
ነገሩ በአደባባይ አይወራም የሚሉ ብዙ ናቸው። ግን የአንሶላ ቅያሪ ጉዳይ የሁላችንንም ደጅ ያንኳኳል። ብዙዎች በምን ያህል ቀናት አንሶላ ይቀየር? በሚለው ቁጥር ላይ አይስማሙም። እርስዎ ግን በምን ያክል ጊዜ አንሶላ ያጥባሉ?
በኢትዮጵያ ተግባራዊ የሆነው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ከባለፈው ጋር ሲነጻጸር ምን ያህል ጭማሪ አሳየ?
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ መናሩን በምክንያትነት በመጥቀስ ከአራት ወራት በፊት ባወጣው የዋጋ ተመን ላይ ከሚያዚያ 30/2014 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ማሻሻያ ማድረጉን አሳስታውቋል። መንግሥት ባለፉት አራት ወራት የነዳጅ ዋጋን ለመደጎም ባወጣው ወጪ ከፍተኛ ጫና ላይ መውደቁን ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
በኢትዮጵያ የጠፋ መድኃኒት የሚያፈላልገው መተግበሪያ
"ጤናዎ" የሞባይል መተግበሪያ የጤና ጥበቃ ከፍተኛ ተጠሪ በተገኙበት በሸራተን አዲስ የተመረቀው ከወራት በፊት ነበር፡፡ በአጭሩ ለማስቀመጥ ደንበኛው የሚፈልገው መድኃኒት የት እንዳለ ይጠቁመዋል፡፡ ይህን የሚያደርገው በስልክ መተግበሪያ በመጠቀም ነው፡፡ መጀመርያ ለደንበኛው፣ ካለበት በ500 ሜትር ራዲየስ ያሉ መድኃኒት ቤቶችን ያሳየዋል፡፡ ወይም ደግሞ መድኃኒት ፈላጊዋ ካለችበት ሆና በከተማው ያሉ መድኃኒት ቤቶቹን እያማረጠች በመተግበሪያው በምናብ ፋርማሲዎች ውስጥ ትዘልቃለች፡፡
ፋኖ ማን ነው? በማንስ ይደገፋል?
የትግራይ ኃይሎች ወደ አማራ ክልል ከገቡበት ጊዜ አንስቶ የፋኖ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ስማቸው ይነሳል። በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎችም የሚገኙ ወጣቶች በተለያዩ የፋኖ አደረጃጀቶች ስር በመሆን እና ‘ያላቸውን መሳሪያ በመያዝ’ በጦርነቱ ላይ ተሳታፊ መሆናቸው ይነገራል። ነገር ግን የትግራይ ኃይሎች ከአማራ ክልል መውጣታቸው ከተነገረም በኋላ በፋኖ አደረጃጀት ስር ምልመላዎች እና ስልጠናዎች ይሰጣሉ። ፋኖ የሚለው ስምም በሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና በተለያዩ ጥቃቶች ሲነሳም ተሰምቷል። ቢቢሲ የምስራቅ አማራ ፋኖ እና የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ አመራሮችን አነጋግሯል።
ሊዲያ ሞገስን 'ተደባዳቢ' ያደረጋት ምንድን ነው?
ሊዲያ በትምህርት ቤት ውስጥ በራሷ መንገድ ለመሄድ መሞከሯ እና "ሌሎች የሚሉትን ሁሉ መቀበል" አለመፈለጓ በሌሎች ነቀፋ እንዲቀርብባት፣ ዘለፋን እንድታስተናግድ መነሻ ሆኗል። በትምህርት ቤቱ ተጽዕኖ እንዳላት ከሚነገር ተማሪ ጋር በነበራት አለመግባባት ምክንያት አብዛኛው ተማሪ ከእርሷ ጋር ጓደኛ ለመሆን አይፈለግም ነበር። በዚህም ምክንያት "ምንም የተለየ ነገር ሳይኖረው" በአለባበሷ፣ በጸጉር አሰራሯ 'በማሾፍ' ሌሎች ተማሪዎች እንዲስቁ እርሷ ደግሞ እንድትሸማቀቅ ይደርግ እንደነበር ታስታውሳለች።
አነጋጋሪው ኤሎን መስክ ማነው?
በትዊተር ሰሌዳው ድንገቴ የሆኑ ሐሳቦችን እየጻፈ ዓለምን እያንጫጫ ያለው ኤሎን መስክ ማን ነው?
ሰዎች ለምን ራሳቸውን ስለማጥፋት ያስባሉ?
ራስን ማጥፋት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ ትልቅ የሞት መንስኤ የሚታይ ጉዳይ ነው። በመላው ዓለም በሚገኙ ወጣቶች ዘንድም ሶስተኛው ትልቁ የሞት መንስኤ ራስን ማጥፋት ነው።
ሌላ ዕይታ
የአማራ ክልል የፀጥታ መዋቅሩ ዝግጁ እንዲሆን አዘዘ
የአማራ ክልል የፀጥታ ምክር ቤት ከህወሓት በኩል ሊሰነዘር ይችላል ላለው ወረራ የክልሉ የፀጥታ መዋቅር ዝግጁ እንዲሆን ትዕዛዝ አስተላለፈ። ምክር ቤቱ በመግለጫው በክልሉ ያለው ሰላምና ፀጥታ ሁኔታ መገምገሙን አስታውቆ፣ ህወሓት "በየቀኑ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመ የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት እያነሳሳ በአማራ ክልል ላይ ዳግም ጦርነት አውጇል" ብሏል።
ከኤርትራ ጋር አዋሳኝ በሆኑ ቦታዎች የከባድ መሳሪያ የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
የትግራይ ኃይሎች ከኤርትራ ጋር አዋሳኝ በሆኑት አካባቢዎች ላይ የከባድ መሳሪያ ጥቃት ከፍተው ለአጭር ጊዜ የቆየ ወታደራዊ ግጭት መካሄዱን ታማኝ ምንጮች ለቢቢሲ አረጋገጡ። ጥቃቱ ተፈጸመ የተባለው እሁድ ሚያዚያ 30/2014 ዓ.ም. በራማ እና ባድመ አካባቢ ባለው የኤርትራ ጦር ላይ ሲሆን፣ ጥቃቱን ተከትሎ በትግራይ ኃይሎችና በኤርትራ ጦር መካከል የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተገልጿል።
ከከፋው የአሲድ ጥቃት በኋላም ስጋት ውስጥ ያለችው ሰላማዊት
በአማራ ክልል በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በቀራኒዮ ከተማ ይኼነው ፈንታ በተባለ ግለሰብ የአሲድ ጥቃት የደረሰባት ሰላማዊት ጊዜው፤ አሁንም ከጥቃት አድራሹ ለእሷ እና ቤተሰቧ ማስፈራሪያ እንደሚደርስ ትናገራለች።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጦር ወንጀል ማስረጃ እንዲጠፋ ተባብሯል መባሉን አጣጣለ
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በምዕራብ ትግራይ የትግራይ ተወላጆች በጅምላ መቀበራቸውን የሚያሳይ የጦር ወንጀል ለመደበቅ የአማራ ሚሊሻዎችን ረድቷል የሚለውን ሪፖርት አጣጣለ።
‘ሲጨንቀን ከሐኪም የማይጠበቅ ምክር እንሰጣለን' - በዓይደር ሆስፒታል የካንሰር ሕክምና ባለሙያ
ለ17 ወራት በቀጠለው ጦርነት ምክንያት በክልሉ የሚገኙ የካንሰር ህሙማን ከባድ ችግር ላይ ወድቀው ከሚገኙ ታካሚዎች መካከል ይጠቀሳሉ። ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ባሉ ጊዜያት 1643 አዋቂዎች እና 126 ህጻናት የካንሰር ታካሚዎች ወደ ሆስፒታሉ መምጣታቸው የሚያሳየው የሆስፒታሉ ሪፖርት፣ አብዛኛዎቹ ግን በትራንስፖርት ችግር፣ በገንዘብ ማጣት እና የስልክ አገልግሎት ባለመኖሩ ምክንያት መጥተው ህክምና ማግኘት አልቻሉም ይላል ሆስፒታሉ።
ህወሓት ለመዝመት ፍቃደኛ ያልሆኑ ልጆች ወላጆችን እያሰረ መሆኑ ተነገረ
ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ጦርነት ውስጥ የገባው ህወሓት እየተካሄደ ባለው ጦርነት ልጆቻቸው ያልዘመቱ ወላጆችን እያሰረ እንደሚገኝ የቤተሰብ አባላት ለቢቢሲ ተናገሩ። ህወሓት በበኩሉ ከዚህ በፊት ልጆች ለምን አልዘመቱም በሚል ወላጆችን የማሰር ምልክቶች ቢኖሩም አሁን ላይ ግን ይህ ቆሟል ይላል።
ቪዲዮ, “ከደረሰብኝ ጥቃት አንፃር ልጄን ሌላ ሰው ወስዶት ስለእናቱ ታሪክ ሳያውቅ እንዲያድግ እመኛለሁ", ርዝመት 3,20
“ከደረሰብኝ ጥቃት አንፃር ልጄን ሌላ ሰው ወስዶት ስለእናቱ ታሪክ ሳያውቅ እንዲያድግ እመኛለሁ"
እንግሊዝኛን ከቢቢሲ ይማሩ
ማጠቃለያ፡ደረጃዎ የትም ጋር ቢሆን በየሳምንቱ አዳዲስ ክፍሎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ።
"የእንግሊዝ መንግሥት ወደ አምባገነኗ ሩዋንዳ ይልከኝ ይሆን? “ ኤርትራዊው ታዳጊ
ለቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ፕሮግራም ወደ ካሌ ከተማ ሳቀና ስደተኞች በሚበዙባት በዚህች የወደብ ከተማ ቁማር ቤት አያለሁ ብዬ አልጠበቅኩም ነበር።
ኢትዮጵያ ውስጥ 'ለመዝናናት' የሚደረግ አደን አለ? እንዴትስ ይከናወናል?
የዱር እንስሳትን በሕጋዊም ሆነ በሕገ-ወጥ መልኩ አድኖ መያዝ ወይም ለምግብነት ማዋል ለረዥም ዓመታት ከሰው ልጅ ጋር የዘለቀ ተግባር ነው።