BBC News, አማርኛ - ዜና

እንዳያመልጥዎ

አነጋጋሪ ጉዳይ

ከየፈርጁ

  • በኢትዮጵያ በመንግሥት ኃይሎች የሚፈጸሙ ሰዎችን የመሰወር ድርጊት እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ

    ኢሰመኮ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ሰዎችን አስገድዶ የመሰወር ድርጊት በአፋጣኝ እንዲቆም ጠየቀ። የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “ይህ አስከፊ የሆነ የአስገድዶ መሰወር ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም መንግሥት አስፈላጊውን ጊዜያዊ እና ዘለቄታዊ እርምጃዎች እንዲወስድ” ጥሪ አቅርበዋል።

    እስረኞች
  • ያድምጡ, ቢቢሲ አማርኛ ዜና

    ‎20:29 EAT - 20:44 EAT

  • ነዳጅ አምራች

    ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቴን እቀንሳለሁ ማለቷ የነዳጅ ዋጋን ከፍ አደረገ

    የዓለም ነዳጃ አምራች ሀገራት የነዳጅን ዋጋን ለማሳደግ በማሰብ የምርት አቅርቦታቸውን ለመቀነስ ተስማምተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በቀጣዩ ሀምሌ ወር በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ ከምርት አቅርቦቷ ላይ እንደምትቀነስ የገለጸች ሲሆን የነዳጅ ላኪዎች ሀገራት ማህበር ወይም ኦፔክ ፕላስ ደግሞ እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 ዕለታዊ የነዳጅ አቅርቦት በ1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ ገልጿል።

  • ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም

    በምሥራቅ ጎጃም ደብረ ኤልያስ ስለተከሰተው እስካሁን የምናውቀው

    በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው ነበር ያላቸው 200 ታጣቂዎች መደምሰሳቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ቅዳሜ ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በመከላከያ ሠራዊት እና በአማራ ክልል የፀጥታ ኃይሎች ተወሰደ በተባለው እርምጃ በቅርቡ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ እንቅስቃሴ መጀመሩን የገለጸው በእስክንድር ነጋ የሚመራ ታጣቂ ቡድን በአካባቢው ይንቀሳቀስ እንደነበር ግብር ኃይሉ ገልጿል።

  • ሩሲያ፤ ከዩክሬን የተቃጣባትን ከባድ ጥቃት መመከቷን አስታወቀች

    ሩሲያ፤ ከዩክሬን የተቃጣባትን ከባድ ጥቃት መመከቷን አስታወቀች

    የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ከባድ የዩክሬን ጥቃት መከላከሉንና 250 ዩክሬናዊያንን መግደሉን ገለጸ።

  • ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን

    ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ሩሲያ “ታሪካዊ ኃላፊነቷን” እንድትወጣ ፕሬዝዳንት ፑቲንን ጠየቁ

    በሩሲያ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሩሲያ “ታሪካዊ ኃላፊነቷን” እንድትወጣ መጠየቃቸውን የአገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ገለጸ።

  • ታላቁ አንዋር መስጂድ

    በአዲስ አበባ የጁመዓ ጸሎትን ተከትሎ በተከሰተ “ረብሻ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ” ተነገረ

    በታላቁ አንዋር መስጂድ የጁመዓ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ ተነሳ ባለው “ረብሻ የሦስት ሰዎች ሕይወት” ማለፉን የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አርብ ምሽት ባወጣው መግለጫ አሳወቀ። ግብረ ኃይሉ ረብሻው “ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱ” ያላቸው በስም ያልተጠቀሱ ቡድኖች የፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ለማድረስ የፈጠሩት ነው ሲል ከሷል።

  • titanic

    ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግዙፏን ታይታኒክን ለመረዳት የሚደረገው ጥረት

    ስለ ዝነኛዋ ታይታኒክ መርከብ አጠቃላይ ሁኔታ እና ስለ ደረሰባት አደጋ ለማወቅ ከ100 ዓመት በኋላ በጥበብ እና በምርምር ሥራዎች ጥረት እየተደረገ ነው። የሰመጠችው ግዙፍ መርከብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ 3 ሺህ 8 መቶ ሜትር ቦታ ላይ ትገኛለች። ታይታኒክን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃላይ ገጽታዋን በመገንባት መርከቧ የበለጠ እንድትታወቅ እየተደረገ ነው። ይህ የዲጂታል ገጽታ በ1912 (እአአ) የሰጠመችውን ታይታኒክ አጠቃላይ ይዘት ለማወቅ እንዲሁም የአደጋውን መንስኤ እና ጉዳት ለመገንዘብ ያግዛል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።

  • ራያን ሬይኖልድስ፣ ሻኪራ፣ ማርቲኔዝ

    ባለፉት ወራት በእግር ኳሱ ዓለም ከታዩ አነጋጋሪ ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹ

    ክሪስቲያኖ ሮናልዶ፤ ፒርስ ሞርጋን ከተሰኘው ጋዜጠኛ ጋር ካደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ጀምሮ እስከ አርጀንቲው ግብ ጠባቂ የዶሃ ድርጊትን ጨምሮ ባለንበት የአውሮፓውያኑ 2023 በስፖርቱ ዙሪያ ብዙ ክስተቶች ተመዝግበዋል። የሆሊውድ ተዋንያን የሆኑት ራያን ሬይኖልድስ እና ሮብ ማኬልኒ የገዙት ክለብ ስኬታማነት ብዙዎችን አጀብ አሰኝቷል። እነሆ በ2023 በእግር ኳሱ ዓለም አነጋገሪ የተባሉ ክስተቶችን በቅንጭቡ መልሰን እንቃኛለን።

  • ሰው ሰራሽ የጦር አውሮፕላን (ድሮን_

    አሜሪካ “በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚታገዝ ድሮን የገዛ ተቆጣጣሪውን ተኩሶ ገድሏል” የሚለውን ዜና አስተባበለች

    የአሜሪካ አየር ኃይል በሰው ሠራሽ የሚታገዝ ሰው ሠራሽ የጦር አውሮፕላን (ድሮን) ከርቀት ቁጥጥር ጣቢያ ያለውን የራሱን ተቆጣጣሪ (Operator) ተኩሶ ገድሏል የሚባለው ዜና ሐሰት ነው ሲል አስተባበለ።

አጃኢብ!

የተመለሱ ጥያቄዎች

  • ሥራችንን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) ልንነጠቅ እንችላለን?

    የቴክኖሎጂ እያደር መምጠቅ ዕድል ብቻ ሳይሆን ስጋትንም ይዞ መጥቷል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት (የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ኤአይ) እድገት የዓለም ኃያላን መንግሥታትን ጭምር ስጋት ውስጥ ከትቷል።

    የቴክኖሎጂ እያደር መምጠቅ ዕድል ብቻ ሳይሆን ስጋትንም ይዞ መጥቷል።
  • ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሐይቅ በሚገኝ መጠለያ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች

    “የምንቀምሰው ባለመኖሩ የተረዳነውን ድስት ሳይቀር ለመሸጥ ተገደናል” በአማራ ክልል ያሉ ተፈናቃዮች

    መሐመድ ሰይድ ይባላሉ። ኑሯቸውን በደቡብ ወሎ ዞን፣ ሐይቅ ከተማ አካባቢ በሚገኝ ቱርክ ካምፕ ተብሎ በሚጠራው የተፈናቃዮች መጠለያ ካደረጉ ሰባት ወራት ተቆጥረዋል። በጊዜያዊ መጠለያው ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ መሐመድ፣ የሚደረግላቸው ድጋፍ ከተቋረጠ ሁለት ወራት መቆጠሩን ይናገራሉ።

  • ኤታክሲያ

    ብዙም ስላልተለመደው ኤታክሲያ ስለተባለው የጤና ችግር ምን ያውቃሉ?

    ታሉላህ ክላርክ በልጅነቷ ከሌሎች ጓደኞቿ የተለየች እንደሆነች ይሰማት ነበር። በ14 ዓመቷ ያልተለመደ አረማመዷን ተከትሎ ሰዎች 'ሰክረሻል እንዴ?' ይሏት ነበር። እንዲያም ሆኖ ግን ኤታክሲያ የተባለው በሽታ እንዳለባት ለማወቅ ስምንት ዓመታት ወስዶባታል። ኤታክሲያ ስለተባለው የጤና እክል ሰምተው ያውቃሉ? ኤታክሲያ ምንድን ነው? ከዚህ ብዙም ካልተለመደ የጤና ችግር ጋር እየኖረች ያለችው ክላርክ ስለ በሽታው እና ከኤታክሲያ ጋር መኖር ምን እንደሚመስል ታስረዳናለች።

  • ራህዋ

    ከባባድ የጦር ወንጀል ሲፈጸም የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ፌስቡክ ለምን ይሰርዛቸዋል?

    ከባባድ የጦር ወንጀል ሲፈጸም የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ፌስቡክ ለምን ይሰርዛቸዋል?

  • በቡታጅራ የትራፊክ አደጋ የገጠመው መኪና እየተጎተተ

    ዝቅተኛ የተሽከርካሪዎች ቁጥር ባላት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ ለምን?

    ኢትዮጵያ የመኪና አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ከሚገኝባቸዉ አገራት መካከል አንዷ ነች። በአገሪቱ እየተስፋፉ ካሉ መንገዶች ጋር በተያያዘም በፍጥነት ማሽከርከር ለአደጋ መንስኤ ከሚሆኑ ነገሮች ቀዳሚ ሆኖ ይጠቃሳል። ለዚህም ይመስላል በኢትዮጵያ የሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች አብዛኛው ምቹ በሆኑ መንገዶች ላይ የሚከሰቱት። ከሌሎች አገራት አንጻር በኢትዮጵያ ያለው የተሽከርካሪዎች ቁጥር ዝቅተኛ ቢሆንም፣ እያጋጠመ ያለው የትራፊክ አደጋ ግን ከፍተኛ ነው። ለምን?

  • ኤርዶዋን ሁለተኛውን ዙር ምርጫ ያሸንፋሉ ተብለው ይጠበቃል

    ዶናት ጋጋሪው፣ የሎሚ ጭማቂ አዟሪው፣ ሰሊጥ ቸርቻሪው ጣይብ ኤርዶዋን ማን ናቸው?

    ለቱርካውያን ከማል አታቱርክን የሚያህል አገር ያቀና የፖለቲከኛ የለም። ከከማል ቀጥሎ ቱርክ ላይ ትልቅ አሻራ ያኖሩት ጣይብ ኤርዶዋን ሆነዋል። በ20 ዓመት የሥልጣን ዘመናቸው በዘመናዊው ዓለም ውስጥ ቱርክ ታሪኳን የሚመጥን ቦታ እንድትይዝ አስችለዋል። ኤርዶዋን ለተጨማሪ የመሪነት ዘመን ለምርጫ ቀርበው ከግማሽ በላይ ድምጽ ባለመገኘቱ፣ ዛሬ ሁለተኛው ዙር ምርጫ ይደረጋል። ለመሆኑ ኤርዶዋን ከየት ተነስተው እዚህ ደረሱ?

  • የሩሲያን ድንበር ሰብረው የገቡት ታጣቂዎች ማንነት እያነጋገረ ነው

    የሩሲያን ድንበር ደፍረው በመሻገር ፑቲንን እየተዋጉ ያሉት ሚሊሻዎች ማን ናቸው?

    የሩሲያን ድንበር ደፍረው በመሻገር ፑቲንን እየተዋጉ ያሉት ሚሊሻዎች ማን ናቸው?

  • ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ

    የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ ቤተሰቦች ጥያቄ እና የንጉሣውያኑ ቤተ መንግሥት ምላሽ

    በ19ኛው ክፍለ ዘመን ከአባቱ ሞት በኋላ ወደ እንግሊዝ የተወሰደው ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ፣ ቤተሰቡን እና አገሩን ድጋሚ የማየት ዕድል ሳይገጥመው ነበር ሕይወቱ እዚያው በለጋነት ዕድሜው ያለፈው። ሥርዓተ ቀብሩም የብሪታኒያ ነገሥታት ከሚያርፉበት ለንደን ከሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ተፈጽሟል። የልዑሉ ህልፈት በርካታ ትውልዶችን ያሳለፈ ቢሆንም ቤተሰቦቹ እና ኢትዮጵያውያን አጽም ወደ አገሩ እንዲመለስ ሲጠይቁ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የልዑል ዓለማየሁ ቤተሰቦች ንጉሥ ቻርልስ ሦስተኛ ጥያቄያቸውን እንደሚመልሱላቸው ተስፋ አድርገዋል። ቢቢሲ ጥያቄውን ለባኪንግሃም ቤተ መንግሥት አቅርቦ ምላሽ አግኝቷል።

  • የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ

    የትግራይ አባቶች ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለመመለስ ምን ይላሉ?

    በትግራይ የተቀሰቀውን ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በትግራይ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት መካከል የነበረው ግንኙነት ሻክሯል። በቅርቡም የትግራይ አባቶች ኤጲስ ቆጶሳትን እንደሚሾሙ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ደግሞ ከትግራይ አባቶች ጋር የተቋረጠውን ግንኙነት ለማደስ አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አዟል። በትግራይ አባቶች በኩል ያለውን አቋም ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ገልጸዋል።

  • ሴቶች

    በኢትዮጵያ ሴቶች ቸል ስለሚሉት የካንሰር ዓይነት ምን ያህል ያውቃሉ?

    በኢትዮጵያ ውስጥ በማሕፀን በር ካንሰር ምክንያት በዓመት 5000 ሴቶች ይሞታሉ። የሞታቸው ዋነኛ ምክንያት ደግሞ ቀድሞ በማወቅ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ተገቢውን ሕክምና አለማግኘታቸው መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ይገልጻል። በተጨማሪም ሴቶች ስለበሽታው በቂ ግንዛቤ ስለሌላቸው የሕክምና ክትትል ቀድመው እንደማይጀምሩ ይነገራል። ይህ የካንሰር አይነት የመከላከያ ክትባት ያለው ሲሆን፣ ከተከሰተ በኋላም በጊዜ ታውቆ ህክምና ከተገኘ መፍትሔ እና ፈውስ ይኖረዋል።

ሌላ ዕይታ

  • የመንግሥት እና የሃይማኖቶች ፍጥጫ በኢትዮጵያ

    አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሃይማኖት ጋር የጠበቀ ግንኙነት አለው። ባለፉት 50 ዓመታት መንግሥት እና ሃይማኖት ድንበራቸው በሕግ የተለየ ቢሆንም፣ በተለያዩ ወቅቶች መንግሥት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ጣልቃ የመግባት ትችት ሲሰነዘርበት ታይቷል። ይህ ሁኔታም ለፍጥጫ እና ለግጭት ምክንያት ሆኗል። የመንግሥት እና የእምነቶች ግንኙነት በአግባቡ ካልተያዘ በተለያዩ ቀውሶች እየተናጠች ያለችውን አገር አደጋ ላይ ሊጥላት እንደሚችል የሚያስጠነቅቁ ብዙ ናቸው። የሁለቱ ግንኙነት እንዴት ነው መሆን ያለበት?

    ፖሊስ እና ተቃዋሚዎች
  • የፈረሰ ቤት

    በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ከ111 ሺህ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን ኢሰመጉ አስታወቀ

    በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው።

  • ጦርነቱን በመሸሽ ወደ ሱዳን የተሰደዱ

    “ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በምዕራብ ትግራይ የዘር ማጽዳት እየተካሄደ ነው” ሂዩማን ራይትስ ዋች

    ሂዩማን ራይትስ ዋች የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት ለማስቆም የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በምዕራብ ትግራይ የዘር ማጽዳት ወንጀል እየተፈጸመ ነው አለ። የመብት ተሟጋቹ የፌደራሉ መንግሥት እና ህወሓት በሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ የቆየውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም ጥቅምት 23/2015 ዓ.ም. የሰላም ስምምነት ከፈረሙ በኋላ የአማራ ኃይሎች ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በተመተባበር የትግራይ ተወላጆች በኃይል ከምዕራብ ትግራይ እንዲለቁ እያደረጉ ነው ብሏል።

  • ባሹ ከሚያስተምራቸው ህጻናት ጋር

    ከትምህርት ለራቁ የዳውሮ ህጻናት እና ጎልማሶች የተስፋ ብርሃንን የፈነጠቀው መምህር

    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞን ውስጥ በሚገኘው ጉኖ ቀበሌ የሚገኘው የሻመና አካባቢ በሁሉም ወራት ለምለም ነው። ከዓመት ዓመት አረንጓዴ ነው። ነገር ግን በአካባቢው በቅርብ ርቀት ትምህርት ቤት የለም። ህጻናት ትምህርት ለመከታተል ከቤታቸው ርቀው መጓዝ ይጠበቅባቸዋል። ርቀት ብቻ ሳይሆን፣ ህጻናቱ ከዚያ ለመድረስ በእነሱ ጉልበት የማይደፈር ፈታኝ መንገድ ይጠብቃቸዋል። ወንዝ ማቋረጥ፣ በማይመቹ እና ገደላማ መንገዶች መጓዝ የግድ ይሆባቸዋል። ያ ደግሞ ለቤተሰብ ጭንቅ ነው። ስለዚህም ያለው አማራጭ ቤት መዋል ብቻ ነው።

  • ናስር አህመድ ለአስር ዓመት ያህል በዚህ የሙያ መስክ ላይ ቆይቶ፣ ዋሻዎችን ተመራምሮ የደረሰብትን ግኝት በመጽሐፍ መልክ ሰንዶ አሳትሞታል።

    በስሙ ዋሻ የተሰየመለት ኢትዮጵያዊው የዋሻዎች ተመራማሪ

    ናስር አሕመድ የዋሻ ፍቅር ያደረበት የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለ ነው። በአገርህን እወቅ ክበብ ለመጀመርያ ጊዜ የተመለከተው ዋሻ በልቡ ውስጥ ተራራ የሚያክል ዋሻ የማሰስ ፍቅርን ዘራ። ቤተሰቡ ግን ሕክምና አጥንቶ ስማቸውን እንዲያስጠራ፣ እግረ መንገዱንም ራሱን አንዲችል ይፈልጉ ነበር። እርሱ ግን ለልቡ ምኞት በብርቱ ታገለ። ፍላጎቱን ተምሮ ሲያሳካም ‘ቢያመው እንጂ ዋሻ ለዋሻ የሚያዞረው በጤናው ቢሆንማ’ ብለው ተዘባብተውበታል። ቢቢሲ ከናስር ጋር ስለሙያው እና ስለ ሕይወቱ ቆይታ አድርጓል።

  • በጥላ ውስጥ ሆና የምትታይ ሴት

    ብዙዎች ከእርኩስ መንፈስ ጋር የሚያመሳስሉት ‘ድንገቴ የልብ ምጥ’ በሽታ ምንድነው?

    በማይቆጣጠሩት ምክንያት፣ ባልተገመተ ሁኔታ እና ባልጠበቁት ጊዜ የልብ መፍረክረክ፣ የእግር መብረክረክ፣ የሰውነት መራድ ይከሰታል። ድንገተኛ ፍርሃት እና ጭንቅ፣ ጥብ ድንገት ደርሶ ይሰፍርብናል። ያለምንም በቂ ምክንያት መሬት ትከዳለች። አንዳንዶች እንደማዞር ያደርጋቸዋል። አንዳንዶች ያቅለሸልሻቸዋል፤ መሬት እንደ እንዝርት ትሾርባቸዋለች።

  • የኢትዮጵያ ባንዲራ እና መዶሻ

    አከራካሪ የሆነው የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት የማሻሻል ጉዳይ

    የኢትዮጵያ ፖሊሲ ኢኒስቲቲዩት ያስጠናው እና ባለፈው ሳምንት ይፋ ያደረገው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጥናት ውጤት ምሑራንን እና ፖለቲከኞችን በደጋፊ እና በነቃፊ ጎራ ለይቶ እያነጋገረ ነው። በዚህ ወቅት የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ማድረግ ‘አገሪቱን ያፈርሳታል’ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ፣ አሁን ትክክለኛው ሰዓት ነው የሚሉ ወገኖችም ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። ተቺዎች የጥናቱ ሥነ ዘዴን ጭምር ሲተቹ፣ የሚደግፉት ደግሞ ወቅታዊ እርምጃ ነው ይላሉ።

  • ፖሰትር

    እንግሊዝኛን ከቢቢሲ ይማሩ

    ማጠቃለያ፡ደረጃዎ የትም ጋር ቢሆን በየሳምንቱ አዳዲስ ክፍሎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ።

  • የቻይና የባሕር ኃይል አባላት

    በአፍሪካ ቀንድ የጦር ሠፈራቸውን የመሠረቱ ኃያላን አገራት

    ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ጂቡቲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያን አንዳንድ ጊዜም ኬንያን የሚያካትተው የአፍሪካ ቀንድ የዓለማችችንን ወሳኝ የባሕር ንግድ መስመርን ይዟል። በርካታ አገራትም በአካባቢው ወታደራዊ ሚና እንዲኖራቸው ይፈልጋሉ። አንዳንዶችም በቀጠናው የጦር ሠፈሮችን አቋቁመው ሠራዊታቸውን አስፍረዋል። አስካሁን ባለው ሁኔታ በአካባቢው ቁልፍ ቦታ ላይ የምትገኘው ጂቡቲ በርካታ አገራትን እያስተናገደች ነው። ሌሎቹስ?

  • በዩኬ የተወለደ ልጅ ከወላጆቹ አንዳቸው ዜግነት ካላቸው ልጁ ዜግነት ያገኛል

    በዩኬ ለልጃቸው የውሸት አባት ለመግዛት ከፍተኛ ገንዘብ የሚከፍሉት ስደተኛ ነፍሰጡሮች

    በርካታ በዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ጥገኝነት ጠያቂ ነፍሰ ጡሮች ለሚለወደው ልጅ የውሸት አባት በመግዛት ቪዛ ለማግኘት እንደሚሞክሩ በቢቢሲ ኒውስናይት የተሠራ የምርመራ ዘገባ አጋለጠ። ድርጊቱ በምን ያህል ጥገኛ ጠያቂዎች የተፈጸመ እንደሆነ ለጊዜው መረጃ ባይኖርም፣ በርካታ ሴቶች በዚህ ዘዴ በዩኬ የመቆያ ቪዛ እንዳገኙ አመላካች ነው ተብሏል። ነፍሰ ጡር እናቶች ለዚህ የውሸት አባት በአማካይ እስከ 10 ሺህ የዩናይትድ ኪንግደም ፓውንድ እንደሚከፍሉ ቢቢሲ ማረጋገጥ ችሏል።