BBC News, አማርኛ - ዜና
እንዳያመልጥዎ
‘የፀጥታ ኃይሎች አስረው ገንዘብ እየተቀበሉ እያንገላቱን ነው’ - የሸገር ከተማ ነዋሪዎች
ሸገር ከተማ ቀድሞ በኦሮምያ የአዲስ አበባ ዙርያ ልዩ ዞን ተብሎ በሚጠሩ የነበሩ ዞኖችን አንድ ላይ በማዋሀድ ከወራት በፊት የተቋቋመ ከተማ ነው። ከተማው ክፍለ ከተማዎች እና ወረዳዎችን በማዋቀር ዋና መቀመጫውን አዲስ አበባ ውስጥ በማድረግ ሥራ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ይሁን እንጂ ዝርፍያ፣ ዛቻ እና ያለ ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰውን ማሰር የተለመደ ሆኗል ይላሉ ቢቢሲ ያነጋገራቸው የከተማዋ ነዋሪዎች። የከተማዋ ባለሥልጣን ግን ይህንን ክስ ያስተባብላሉ።
በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ
ፕሬዚዳንት ካጋሜ ጄነራሎችን ጨምሮ ከ200 በላይ ወታደሮችን አሰናበቱ
የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ የመከላከያ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችን ጨምሮ ከ200 በላይ ወታደሮችን አሰናበቱ።
የሩዋንዳ ዘር ማጥፋት ተጠርጣሪው ፍርድ ቤት ለመቆም ብቁ አይደለም ተባለ
ከአስርታት በፊት ሩዋንዳ ውስጥ የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት በገንዘብ ደግፏል ተብሎ የተከሰሰው የ88 ዓመቱ አዛውንት በጤና ችግር ምክንያት ፍርድ ቤት ለመቆም ብቁ አይደለም ሲል የተባበሩት መንግሥታት ፍርድ ቤት ወሰነ።
የፊቱ ገጽታ ‘አስቀያሚ’ ነው በሚል እናት እና አባቱ የጣሉት ልጅ ፈተና
ወላጆች የልጃቸው ገጽታ ‘አስቀያሚ’ ነው በሚል ልጃቸውን ሊጥሉ ይችላሉ? አዎ፤ ጆኖ ላንካስተር ይህ መጥፎ ሁኔታ አጋጥሞት ከእናት እና ከአባቱ ተለይቶ ነው ያደገው። አጥንት እና ጡንቻ ላይ ጉዳት በሚያደርስ በሽታ ተጠቂ የሆነው ጆኖ፤ በዚህ ምክንያት የፊቱ ገጽታ በመበላሸቱ በተወለደ በሰዓታት ውስጥ ቤተሰቦቹ እንደጣሉት ይናገራል። ከአምስት ዓመቱ ጀምሮ በማደጎ ቤት ቆይቶ ወደ ወጣትነት ዕድሜ የደረሰው ጆኖ፣ ያለፈበትን አሳዛኝ ታሪክ እና ወላጆቹን ለማግኘት ያደረገውን ጥረት ይተርካል።
የዩክሬን ግድብ መመታቱን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ተፈናቀሉ
የዩክሬኑ ግድብ በሩሲያ ድብደባ መፍረሱን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ጎርፍ በመሸሽ ለቀው እየወጡ ነው።
የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኃላፊዎች ከሥራ ለቀቁ መባሉን አስተባበለ
የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ኃላፊዎች ድርጅቱ የሚያካሂደው ምርመራ ከመጠናቀቁ በፊት በፈቃዳቸው ሥራቸውን ለቀዋል የተባለው ሐሰት ነው ሲል ድርጅቱ አስተባበለ።
በሕንድ የባቡር ግጭት ከሞቱ ሰዎች መካከል 80ውን አስክሬኖች መለየት አልተቻለም
ከአምስት ቀናት በፊት በተከሰተውና በሕንድ ታሪክ የከፋው ነው በታለው የባቡር አደጋ ከሞቱ 288 ሰዎች መካከል 80 የሚሆኑትን ሰዎች አስክሬን ሊለይ እንዳልቻለ ተገለጸ።
ኢራን ከዓመታት በኋላ በሳዑዲ የሚገኘው ኤምባሲዋን ዳግም ከፈተች
የመካከለኛው ምሥራቅ ተቀናቃኞች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ካቋረጡ ከሰባት ዓመታት በኋላ ኢራን በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘውን ኤምባሲዋን ከፍታለች። ኤምባሲው በሪያድ ዳግም ሲከፈት የኢራን እና የሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተወካዮች መገኘታቸውን የሳዑዲ መንግሥት ቴሌቪዢን ጣቢያ ዘግቧል።
አነጋጋሪ ጉዳይ
በደብረ ኤልያስ ግጭት ውስጥ ‘የዓለም ብርሃን’ የተሰኘ የእምነት እንቅስቃሴ ተሳታፊ ነበር ተባለ
በአማራ ክልል፣ ምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም ውስጥ ከተከሰተው ግጭት ጋር አዲስ የእምነት እንቅስቃሴ ለማስፋፋት አላማ የነበራቸው መሳተፋቸውን የአካባቢው አስተዳዳሪ ተናገሩ። የደብረ ኤሊያስ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መልካሙ አዲስ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በገዳሙ ውስጥ መሽገው ነበር የተባሉት “‘የዓለም ብርሃን’ የተባለ እምነትን ለማስፋፋት አላማ የነበራቸው” ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ግጭት ውስጥ መግባታቸውን ገልጸዋል።
በእስራኤል ወታደር የተተኮሰበት ፍልስጤማዊ ህጻን ሕይወቱ አለፈ
ከአራት ቀናት በፊት የእስራኤል ጦር ጭንቅላቱ ላይ በተኩስ የመታው የሶስት ዓመት ህጻን ህይወቱ አልፏል። ሞሃመድ ታሚሚ የተባለው ህጻንና ከአባቱ ጋር በእስራኤል ቁጥጥር ስር ባለው ዌስት ባንክ ከሚገኘው ቤታቸው በመውጣት ላይ ሳሉ ነበር የተተኮሰባቸው።
ለሩሲያ ሲሰልል ተይዞ ለእሥር የተዳረገው አሜሪካዊ ሰላይ ማረሚያ ቤት ሞቶ ተገኘ
ለሩሲያ ሲሰልል የተያዘው የአሜሪካው ኤፍቢአይ መኮንን እሥር ቤት ውስጥ ሞቶ ተገኘ። በአሜሪካ የስለላ ታሪካ ከባድ ጥፋት የፈፀመው ሰው ተብሎ የሚጠራው ሮበርት ሃንሰን ጥብቅ በሚባለው የኮሎራዶው ፍሎረንስ እሥር ቤት ነበር።
በብዙዎች የማይታወቀው የ560 ኪሎ ሜትር የበረሃ ላይ የሩጫ ውድድር
ዘ ስፒድ ፕሮጀክት፤ ከሎስ አንጀለስ እስከ ላስ ቬጋስ የሚደረግ፤ እስካሁን ቅጣት ያልተላለፈበት፤ ስፖንሰር የሌለው 563 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የሩጭ ውድድር ነው። ድረ-ገፅ የለውም። ‘እዚህ ይመዝገቡ’ የሚል አማራጭም አልያዘም። ሕግ የለውም። በዚህ ነው መንገዱ የሚል ጥቆማ አይገኝም። ተመልካች ማግኘት ፈፅሞ አይታሰብም። ውድድሩ አንድ ሳምንት እስኪቀረው ምንም ዓይነት መረጃ ማግኘት አዳጋች ነው።
የሐዋሳው የፀጋ በላቸው ጠለፋ የቀሰቀሰው ስጋት እና ጥያቄዎች
ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ እና በመደበኛ የመገናና ብዙኃን ዘንድ በስፋት መነጋገሪያ የነበረው የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ የሆነችው የፀጋ በላቸው መጠለፍ እና ለቀናት የደረሰችበት አለመታወቁ ነበረ። በርካቶች ምስሏን አጋርተዋል። “ፀጋ የት ናት? ፍትህ ለፀጋ” ሲሉ ጠይቀዋል። ግንቦት 24/2015 ዓ.ም. ፀጋ ከአጋቿ ቁጥጥር ነጻ በመውጣት ወደ ሐዋሳ መመለሷን ቤተሰቧ እና የከተማው ፖሊስ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። የከተማዋ ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ግን አሁንም ጥያቄ አላቸው።
የቻይናው የመከላከያ ሚኒስትር ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ጦርነት ‘ለዓለም እልቂት’ ይሆናል አሉ
የቻይና መከላከያ ሚኒስትር ሊ ሻንግፉ አገራቸው ከአሜሪካ ጋር ጦርነት ብትገጥም ዓለም “መቋቋም የማትችለው እልቂት” ይሆናል አሉ።
የሁለት አንጋፋ ፖለቲከኞች ዕይታ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጥረት ዙሪያ
በኢትዮጵያ ለዓመታት የተከማቸውን የፖለቲካ ችግር በውይይት እና በብሔራዊ መግባባት እንዲፈታ ብዙዎች ሲወተውቱ ቆይተዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ በልሂቃን መካከል በአገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት አለመኖሩ በመካከላቸው ያለው አለመተማመን እና ጥርጣሬ የዴሞክራሲ የሽግግር ሂደቱን ፈታኝ አድርጎታል ሲባል ቆይቷል።
በአማራ ክልል አርሶ አደሮች በምርጥ ዘር እና በማዳበሪያ እጦት ለተቃውሞ አደባባይ ወጡ
በአማራ ክልል የሚገኙ አርሶ አደሮች በምርጥ ዘር እና በአፈር ማዳበሪያ እጦት ምክንያት ለተከታታይ ቀናት በክልሉ መዲና ባሕርዳር እና በሌሎችም አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ።
በአሜሪካ ዩታ ግዛት መጽሐፍ ቅዱስ ከመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ታገደ
በአሜሪካ ዩታ ውስጥ በምትገኝ አነስተኛ ግአዛት ውስጥ የሚገኝ አንድ የመጀመርያ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መጽሐፍ ቅዱስን “አመጽ እና ነውር” የያዘ በሚል ከትምህርት ቤቶቹ ውስጥ ማገዱ ተሰምቷል።
በአዲስ አበባ በርካታ ኤርትራውያን ስደተኞች ታስረው እንደነበር ኢሰመኮ ገለጸ
በአዲስ አበባ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራዊያን ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ሰነድ የላችሁም በሚል በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ።
ከየፈርጁ
በኢትዮጵያ በመንግሥት ኃይሎች የሚፈጸሙ ሰዎችን የመሰወር ድርጊት እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ
ኢሰመኮ በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው ሰዎችን አስገድዶ የመሰወር ድርጊት በአፋጣኝ እንዲቆም ጠየቀ። የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “ይህ አስከፊ የሆነ የአስገድዶ መሰወር ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም መንግሥት አስፈላጊውን ጊዜያዊ እና ዘለቄታዊ እርምጃዎች እንዲወስድ” ጥሪ አቅርበዋል።
ያድምጡ, ቢቢሲ አማርኛ ዜና
20:29 EAT - 20:44 EAT
ሳዑዲ አረቢያ የነዳጅ ምርቴን እቀንሳለሁ ማለቷ የነዳጅ ዋጋን ከፍ አደረገ
የዓለም ነዳጃ አምራች ሀገራት የነዳጅን ዋጋን ለማሳደግ በማሰብ የምርት አቅርቦታቸውን ለመቀነስ ተስማምተዋል። ሳዑዲ አረቢያ በቀጣዩ ሀምሌ ወር በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ ከምርት አቅርቦቷ ላይ እንደምትቀነስ የገለጸች ሲሆን የነዳጅ ላኪዎች ሀገራት ማህበር ወይም ኦፔክ ፕላስ ደግሞ እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 ዕለታዊ የነዳጅ አቅርቦት በ1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ ገልጿል።
በምሥራቅ ጎጃም ደብረ ኤልያስ ስለተከሰተው እስካሁን የምናውቀው
በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ደብረ ኤልያስ ወረዳ ሥላሴ ገዳም መሽገው ነበር ያላቸው 200 ታጣቂዎች መደምሰሳቸውን የኢትዮጵያ መንግሥት የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ቅዳሜ ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በመከላከያ ሠራዊት እና በአማራ ክልል የፀጥታ ኃይሎች ተወሰደ በተባለው እርምጃ በቅርቡ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተባለ እንቅስቃሴ መጀመሩን የገለጸው በእስክንድር ነጋ የሚመራ ታጣቂ ቡድን በአካባቢው ይንቀሳቀስ እንደነበር ግብር ኃይሉ ገልጿል።
ሩሲያ፤ ከዩክሬን የተቃጣባትን ከባድ ጥቃት መመከቷን አስታወቀች
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ከባድ የዩክሬን ጥቃት መከላከሉንና 250 ዩክሬናዊያንን መግደሉን ገለጸ።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ሩሲያ “ታሪካዊ ኃላፊነቷን” እንድትወጣ ፕሬዝዳንት ፑቲንን ጠየቁ
በሩሲያ ጉብኝት እያደረጉ ያሉት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ሩሲያ “ታሪካዊ ኃላፊነቷን” እንድትወጣ መጠየቃቸውን የአገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ገለጸ።
በአዲስ አበባ የጁመዓ ጸሎትን ተከትሎ በተከሰተ “ረብሻ የሦስት ሰዎች ሕይወት ማለፉ” ተነገረ
በታላቁ አንዋር መስጂድ የጁመዓ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ ተነሳ ባለው “ረብሻ የሦስት ሰዎች ሕይወት” ማለፉን የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አርብ ምሽት ባወጣው መግለጫ አሳወቀ። ግብረ ኃይሉ ረብሻው “ሃይማኖትን ሽፋን በማድረግ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማፍረስ የሚንቀሳቀሱ” ያላቸው በስም ያልተጠቀሱ ቡድኖች የፀጥታ ኃይሎች ላይ ጉዳት ለማድረስ የፈጠሩት ነው ሲል ከሷል።
ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ግዙፏን ታይታኒክን ለመረዳት የሚደረገው ጥረት
ስለ ዝነኛዋ ታይታኒክ መርከብ አጠቃላይ ሁኔታ እና ስለ ደረሰባት አደጋ ለማወቅ ከ100 ዓመት በኋላ በጥበብ እና በምርምር ሥራዎች ጥረት እየተደረገ ነው። የሰመጠችው ግዙፍ መርከብ በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ 3 ሺህ 8 መቶ ሜትር ቦታ ላይ ትገኛለች። ታይታኒክን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃላይ ገጽታዋን በመገንባት መርከቧ የበለጠ እንድትታወቅ እየተደረገ ነው። ይህ የዲጂታል ገጽታ በ1912 (እአአ) የሰጠመችውን ታይታኒክ አጠቃላይ ይዘት ለማወቅ እንዲሁም የአደጋውን መንስኤ እና ጉዳት ለመገንዘብ ያግዛል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።
ባለፉት ወራት በእግር ኳሱ ዓለም ከታዩ አነጋጋሪ ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹ
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ፤ ፒርስ ሞርጋን ከተሰኘው ጋዜጠኛ ጋር ካደረገው አነጋጋሪ ቃለ ምልልስ ጀምሮ እስከ አርጀንቲው ግብ ጠባቂ የዶሃ ድርጊትን ጨምሮ ባለንበት የአውሮፓውያኑ 2023 በስፖርቱ ዙሪያ ብዙ ክስተቶች ተመዝግበዋል። የሆሊውድ ተዋንያን የሆኑት ራያን ሬይኖልድስ እና ሮብ ማኬልኒ የገዙት ክለብ ስኬታማነት ብዙዎችን አጀብ አሰኝቷል። እነሆ በ2023 በእግር ኳሱ ዓለም አነጋገሪ የተባሉ ክስተቶችን በቅንጭቡ መልሰን እንቃኛለን።
አሜሪካ “በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚታገዝ ድሮን የገዛ ተቆጣጣሪውን ተኩሶ ገድሏል” የሚለውን ዜና አስተባበለች
የአሜሪካ አየር ኃይል በሰው ሠራሽ የሚታገዝ ሰው ሠራሽ የጦር አውሮፕላን (ድሮን) ከርቀት ቁጥጥር ጣቢያ ያለውን የራሱን ተቆጣጣሪ (Operator) ተኩሶ ገድሏል የሚባለው ዜና ሐሰት ነው ሲል አስተባበለ።
አጃኢብ!
ሰው ሰራሽ አስተውሎት የሰው ልጆችን ከምድር ሊያጠፋ ይችላል ሲሉ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ
በኦፕንኤአይ እና ዲፕማይንድ የተባሉ ስመ ጥር የቴክኖሎጂ ተቋማት መሪዎችን ጨምሮ በርካታ ባለሙያዎች ሰው ሰራሽ አስተውሎት (አርተፊሻል ኢንተለጀንስ) የሰው ልጆችን ከምድር ሊያጠፋ ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ።
4 ጨቅላ ልጆቿን ገድላለች የተባለች እናት ከ20 ዓመታት በኋላ ነጻ ወጣች
አራት ጨቅላ ልጆቿን ገድላለች በሚል “የአውስትራሊያዋ አደገኛ ገዳይ” የሚል ስም ወጥቶላት የነበረችው እናት አዲስ ማስረጃ መገኘቱን ተከትሎ ከእስር ነጻ ወጣች።
19 መምህራን ከሞቱበት የመኪና አደጋ ምንም ሳይሆን የተረፈው መምህር የአደጋው የመጨረሻ ቅጽበት ትውስታ
ከሳምንት በፊት በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን የደረሰው አስከፊ የትራፊክ አደጋ የ19 የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞችን ሕይወት ሲቀጥፍ በ18 ሰዎች ላይ ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳትን አደርሷል። የብዙዎችን ሕይወት ከቀጠፈው እና የአካል ጉዳትን ካስከተለው ከዚህ አደጋ ታዲያ ሁለት መምህራን ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በሕይወት መትረፍ ችለዋል። ከእነዚህ መምህራን አንዱ ደግሞ ደስታ ሙላቱ ነው።
ሰው ሲሞት በዘፈን እና በጭፈራ የሚሸኘው የደቡብ ኢትዮጵያው ማኅበረሰብ
ሞት በሁሉም ዘንድ ሁሌም አዲስ ነው። በመጣ ቁጥር የሚያስደነግጥ በብዙ ማኅበረሰቦች ዘንድም ማቅ የሚያስለብስ እና እንባ የሚያራጭ ክስተት ነው። ሟችን ለመሰናበትም ሆነ ቤተሰቡን ለማጽናናት የሚሰበሰበውም ሐዘኑን የሚገልጸው እንባውን እያፈሰሰ፣ ደረቱን እየደቃ ነው። በአንዳንድ አካባቢ ዘመድ የሞተባቸው ቤተሰቦች ጥቁር መልበስ፣ ፀጉር መላጨት እና ወትሮ ሲፈጽሙት ከነበሩ የደስታ ድርጊቶች መታቀብ የተለመደ ነው።
በቁማር ሱስ የሚናውዙት የአውሮፓ ‘ፕሮፌሽናል’ እግር ኳስ ተጫዋቾች
ሳይንቲፊክ ሪፖርትስ ጆርናል በዚህ ዓመት ባስጠናው ጥናት በአየርላንድ ‘ፕሮፌሽናል’ አትሌቶች ከሌላው ጊዜ እጥፍ የቁማር ሱስ እንዳለባቸው አጋልጧል። ተቋሙ ከዚህ ቀደም በ2016 አውሮፓ ያሉ አትሌቶች በቁማር ሱስ እንደናወዙ በጥናቱ ገልጾ ነበር። በ2014 የተሠራ ሌላ ጥናት ደግሞ ወንድ ‘ፕሮፌሽናል’ እግር ኳስ ተጫዋች እና የክሪኬት ተጫዋቾች ከሌለው የሕብረተሰብ ክፍል በበለጠ የቁማር ሱስ ተጠቂዎች መሆናቸውን ጠቁሟል።
የቀድሞው የሩሲያ ሰላይ ነው ተብሎ የተጠረጠረው አሳ ነባሪ በስዊድን የባህር ዳርቻ ላይ ታየ
የቀድሞ የሩሲያ ሰላይ ነው ተብሎ የተጠረጠረው አሳ ነባሪ በስዊድን የባህር ዳርቻ ላይ መታየቱን ቤሉጋ አሳነባሪን ለመከታተል የሚሰራው ድርጅት አስታወቀ።
የተመረዘ ገንፎ የበሉ 13 ናሚቢያዊያን የአንድ የቤተሰብ አባላት ሕይወታቸው አለፈ
በአፍሪካዊቷ ሃገር በሶስት ቀናት ውስጥ 13 የአንድ ቤተሰብ ሰዎች በምግብ መመዘረዝ ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል።
አሜሪካ ከምዕተ ዓመታት በፊት በጥንቆላ ወንጅላ የገደለቻቸውን ግለሰቦች ስም ነጻ አደረገች
በአሜሪካዋ ኮነቲኬት ግዛት ከ370 ዓመታት በፊት በጥንቆላ ተግባር ጥፋተኛ ተብለው የነበሩ ግለሰቦች ከጥፋታቸው ነጻ እንዲባሉ ምክር ቤቱ ወሰነ።
በሰው አንጎል ውስጥ ‘ቺፕ’ የሚቀብረው የኢላን መስክ ኩባንያ በሰው ላይ ሙከራ ሊያደርግ ነው
ኒውራሊንክ የተባለው በሰው አንጎል ውስጥ ‘ቺፕ’ የሚቀብረው የኢላን መስክ ድርጅት በሰው ልጅ ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ተፈቀደለት።
‘ቲክቶከሯ’ በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተጫዋቾችን ላይ ለፈጸመችው ጥፋት ፍርድ ቤት ቀረበች
ኦርላ ሜሊሳ የተባለች የቪዲዮ ማጋሪያ የሆነው የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ ቲክቶክ ተሳታፊ፣ በታዋቂ የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ተጫዋቾች ላይ ለፈጠረችው ጫና ፍርድ ቤት ቀረበች።
የተመለሱ ጥያቄዎች
ሥራችንን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) ልንነጠቅ እንችላለን?
የቴክኖሎጂ እያደር መምጠቅ ዕድል ብቻ ሳይሆን ስጋትንም ይዞ መጥቷል። የሰው ሰራሽ አስተውሎት (የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ኤአይ) እድገት የዓለም ኃያላን መንግሥታትን ጭምር ስጋት ውስጥ ከትቷል።
“የምንቀምሰው ባለመኖሩ የተረዳነውን ድስት ሳይቀር ለመሸጥ ተገደናል” በአማራ ክልል ያሉ ተፈናቃዮች
መሐመድ ሰይድ ይባላሉ። ኑሯቸውን በደቡብ ወሎ ዞን፣ ሐይቅ ከተማ አካባቢ በሚገኝ ቱርክ ካምፕ ተብሎ በሚጠራው የተፈናቃዮች መጠለያ ካደረጉ ሰባት ወራት ተቆጥረዋል። በጊዜያዊ መጠለያው ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንደሚገኙ የገለጹት አቶ መሐመድ፣ የሚደረግላቸው ድጋፍ ከተቋረጠ ሁለት ወራት መቆጠሩን ይናገራሉ።
ብዙም ስላልተለመደው ኤታክሲያ ስለተባለው የጤና ችግር ምን ያውቃሉ?
ታሉላህ ክላርክ በልጅነቷ ከሌሎች ጓደኞቿ የተለየች እንደሆነች ይሰማት ነበር። በ14 ዓመቷ ያልተለመደ አረማመዷን ተከትሎ ሰዎች 'ሰክረሻል እንዴ?' ይሏት ነበር። እንዲያም ሆኖ ግን ኤታክሲያ የተባለው በሽታ እንዳለባት ለማወቅ ስምንት ዓመታት ወስዶባታል። ኤታክሲያ ስለተባለው የጤና እክል ሰምተው ያውቃሉ? ኤታክሲያ ምንድን ነው? ከዚህ ብዙም ካልተለመደ የጤና ችግር ጋር እየኖረች ያለችው ክላርክ ስለ በሽታው እና ከኤታክሲያ ጋር መኖር ምን እንደሚመስል ታስረዳናለች።
ከባባድ የጦር ወንጀል ሲፈጸም የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ፌስቡክ ለምን ይሰርዛቸዋል?
ከባባድ የጦር ወንጀል ሲፈጸም የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ፌስቡክ ለምን ይሰርዛቸዋል?
ዝቅተኛ የተሽከርካሪዎች ቁጥር ባላት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የትራፊክ አደጋ ለምን?
ኢትዮጵያ የመኪና አደጋ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ከሚገኝባቸዉ አገራት መካከል አንዷ ነች። በአገሪቱ እየተስፋፉ ካሉ መንገዶች ጋር በተያያዘም በፍጥነት ማሽከርከር ለአደጋ መንስኤ ከሚሆኑ ነገሮች ቀዳሚ ሆኖ ይጠቃሳል። ለዚህም ይመስላል በኢትዮጵያ የሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች አብዛኛው ምቹ በሆኑ መንገዶች ላይ የሚከሰቱት። ከሌሎች አገራት አንጻር በኢትዮጵያ ያለው የተሽከርካሪዎች ቁጥር ዝቅተኛ ቢሆንም፣ እያጋጠመ ያለው የትራፊክ አደጋ ግን ከፍተኛ ነው። ለምን?
ዶናት ጋጋሪው፣ የሎሚ ጭማቂ አዟሪው፣ ሰሊጥ ቸርቻሪው ጣይብ ኤርዶዋን ማን ናቸው?
ለቱርካውያን ከማል አታቱርክን የሚያህል አገር ያቀና የፖለቲከኛ የለም። ከከማል ቀጥሎ ቱርክ ላይ ትልቅ አሻራ ያኖሩት ጣይብ ኤርዶዋን ሆነዋል። በ20 ዓመት የሥልጣን ዘመናቸው በዘመናዊው ዓለም ውስጥ ቱርክ ታሪኳን የሚመጥን ቦታ እንድትይዝ አስችለዋል። ኤርዶዋን ለተጨማሪ የመሪነት ዘመን ለምርጫ ቀርበው ከግማሽ በላይ ድምጽ ባለመገኘቱ፣ ዛሬ ሁለተኛው ዙር ምርጫ ይደረጋል። ለመሆኑ ኤርዶዋን ከየት ተነስተው እዚህ ደረሱ?
የሩሲያን ድንበር ደፍረው በመሻገር ፑቲንን እየተዋጉ ያሉት ሚሊሻዎች ማን ናቸው?
የሩሲያን ድንበር ደፍረው በመሻገር ፑቲንን እየተዋጉ ያሉት ሚሊሻዎች ማን ናቸው?
የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ ቤተሰቦች ጥያቄ እና የንጉሣውያኑ ቤተ መንግሥት ምላሽ
በ19ኛው ክፍለ ዘመን ከአባቱ ሞት በኋላ ወደ እንግሊዝ የተወሰደው ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ፣ ቤተሰቡን እና አገሩን ድጋሚ የማየት ዕድል ሳይገጥመው ነበር ሕይወቱ እዚያው በለጋነት ዕድሜው ያለፈው። ሥርዓተ ቀብሩም የብሪታኒያ ነገሥታት ከሚያርፉበት ለንደን ከሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ተፈጽሟል። የልዑሉ ህልፈት በርካታ ትውልዶችን ያሳለፈ ቢሆንም ቤተሰቦቹ እና ኢትዮጵያውያን አጽም ወደ አገሩ እንዲመለስ ሲጠይቁ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት የልዑል ዓለማየሁ ቤተሰቦች ንጉሥ ቻርልስ ሦስተኛ ጥያቄያቸውን እንደሚመልሱላቸው ተስፋ አድርገዋል። ቢቢሲ ጥያቄውን ለባኪንግሃም ቤተ መንግሥት አቅርቦ ምላሽ አግኝቷል።
የትግራይ አባቶች ወደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለመመለስ ምን ይላሉ?
በትግራይ የተቀሰቀውን ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በትግራይ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት መካከል የነበረው ግንኙነት ሻክሯል። በቅርቡም የትግራይ አባቶች ኤጲስ ቆጶሳትን እንደሚሾሙ አስታውቀዋል። በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ደግሞ ከትግራይ አባቶች ጋር የተቋረጠውን ግንኙነት ለማደስ አስፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አዟል። በትግራይ አባቶች በኩል ያለውን አቋም ብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ሴቶች ቸል ስለሚሉት የካንሰር ዓይነት ምን ያህል ያውቃሉ?
በኢትዮጵያ ውስጥ በማሕፀን በር ካንሰር ምክንያት በዓመት 5000 ሴቶች ይሞታሉ። የሞታቸው ዋነኛ ምክንያት ደግሞ ቀድሞ በማወቅ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ተገቢውን ሕክምና አለማግኘታቸው መሆኑን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ይገልጻል። በተጨማሪም ሴቶች ስለበሽታው በቂ ግንዛቤ ስለሌላቸው የሕክምና ክትትል ቀድመው እንደማይጀምሩ ይነገራል። ይህ የካንሰር አይነት የመከላከያ ክትባት ያለው ሲሆን፣ ከተከሰተ በኋላም በጊዜ ታውቆ ህክምና ከተገኘ መፍትሔ እና ፈውስ ይኖረዋል።
ሌላ ዕይታ
የመንግሥት እና የሃይማኖቶች ፍጥጫ በኢትዮጵያ
አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሃይማኖት ጋር የጠበቀ ግንኙነት አለው። ባለፉት 50 ዓመታት መንግሥት እና ሃይማኖት ድንበራቸው በሕግ የተለየ ቢሆንም፣ በተለያዩ ወቅቶች መንግሥት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ጣልቃ የመግባት ትችት ሲሰነዘርበት ታይቷል። ይህ ሁኔታም ለፍጥጫ እና ለግጭት ምክንያት ሆኗል። የመንግሥት እና የእምነቶች ግንኙነት በአግባቡ ካልተያዘ በተለያዩ ቀውሶች እየተናጠች ያለችውን አገር አደጋ ላይ ሊጥላት እንደሚችል የሚያስጠነቅቁ ብዙ ናቸው። የሁለቱ ግንኙነት እንዴት ነው መሆን ያለበት?
በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች ከ111 ሺህ በላይ ቤቶች መፍረሳቸውን ኢሰመጉ አስታወቀ
በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተሞች እየተካሄደ ነው ባለው የቤት ፈረሳ እና የግዳጅ የማስነሳት ሂደት 111 ሺህ 811 ቤቶች መፍረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) አስታወቀ። ኢሰመጉ ይህንን የገለጸው ከጥቅምት 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በጉዳዩ ላይ ያካሄደውን የምርመራ ሪፖርት ግንቦት 23/2015 ዓ.ም. ይፋ ባደረገበት ጊዜ ነው።
“ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በምዕራብ ትግራይ የዘር ማጽዳት እየተካሄደ ነው” ሂዩማን ራይትስ ዋች
ሂዩማን ራይትስ ዋች የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት ለማስቆም የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ በምዕራብ ትግራይ የዘር ማጽዳት ወንጀል እየተፈጸመ ነው አለ። የመብት ተሟጋቹ የፌደራሉ መንግሥት እና ህወሓት በሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ የቆየውን የእርስ በርስ ጦርነት ለማስቆም ጥቅምት 23/2015 ዓ.ም. የሰላም ስምምነት ከፈረሙ በኋላ የአማራ ኃይሎች ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በተመተባበር የትግራይ ተወላጆች በኃይል ከምዕራብ ትግራይ እንዲለቁ እያደረጉ ነው ብሏል።
ከትምህርት ለራቁ የዳውሮ ህጻናት እና ጎልማሶች የተስፋ ብርሃንን የፈነጠቀው መምህር
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳውሮ ዞን ውስጥ በሚገኘው ጉኖ ቀበሌ የሚገኘው የሻመና አካባቢ በሁሉም ወራት ለምለም ነው። ከዓመት ዓመት አረንጓዴ ነው። ነገር ግን በአካባቢው በቅርብ ርቀት ትምህርት ቤት የለም። ህጻናት ትምህርት ለመከታተል ከቤታቸው ርቀው መጓዝ ይጠበቅባቸዋል። ርቀት ብቻ ሳይሆን፣ ህጻናቱ ከዚያ ለመድረስ በእነሱ ጉልበት የማይደፈር ፈታኝ መንገድ ይጠብቃቸዋል። ወንዝ ማቋረጥ፣ በማይመቹ እና ገደላማ መንገዶች መጓዝ የግድ ይሆባቸዋል። ያ ደግሞ ለቤተሰብ ጭንቅ ነው። ስለዚህም ያለው አማራጭ ቤት መዋል ብቻ ነው።
በስሙ ዋሻ የተሰየመለት ኢትዮጵያዊው የዋሻዎች ተመራማሪ
ናስር አሕመድ የዋሻ ፍቅር ያደረበት የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እያለ ነው። በአገርህን እወቅ ክበብ ለመጀመርያ ጊዜ የተመለከተው ዋሻ በልቡ ውስጥ ተራራ የሚያክል ዋሻ የማሰስ ፍቅርን ዘራ። ቤተሰቡ ግን ሕክምና አጥንቶ ስማቸውን እንዲያስጠራ፣ እግረ መንገዱንም ራሱን አንዲችል ይፈልጉ ነበር። እርሱ ግን ለልቡ ምኞት በብርቱ ታገለ። ፍላጎቱን ተምሮ ሲያሳካም ‘ቢያመው እንጂ ዋሻ ለዋሻ የሚያዞረው በጤናው ቢሆንማ’ ብለው ተዘባብተውበታል። ቢቢሲ ከናስር ጋር ስለሙያው እና ስለ ሕይወቱ ቆይታ አድርጓል።
ብዙዎች ከእርኩስ መንፈስ ጋር የሚያመሳስሉት ‘ድንገቴ የልብ ምጥ’ በሽታ ምንድነው?
በማይቆጣጠሩት ምክንያት፣ ባልተገመተ ሁኔታ እና ባልጠበቁት ጊዜ የልብ መፍረክረክ፣ የእግር መብረክረክ፣ የሰውነት መራድ ይከሰታል። ድንገተኛ ፍርሃት እና ጭንቅ፣ ጥብ ድንገት ደርሶ ይሰፍርብናል። ያለምንም በቂ ምክንያት መሬት ትከዳለች። አንዳንዶች እንደማዞር ያደርጋቸዋል። አንዳንዶች ያቅለሸልሻቸዋል፤ መሬት እንደ እንዝርት ትሾርባቸዋለች።
አከራካሪ የሆነው የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት የማሻሻል ጉዳይ
የኢትዮጵያ ፖሊሲ ኢኒስቲቲዩት ያስጠናው እና ባለፈው ሳምንት ይፋ ያደረገው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጥናት ውጤት ምሑራንን እና ፖለቲከኞችን በደጋፊ እና በነቃፊ ጎራ ለይቶ እያነጋገረ ነው። በዚህ ወቅት የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ማድረግ ‘አገሪቱን ያፈርሳታል’ የሚሉ እንዳሉ ሁሉ፣ አሁን ትክክለኛው ሰዓት ነው የሚሉ ወገኖችም ድምጻቸውን እያሰሙ ነው። ተቺዎች የጥናቱ ሥነ ዘዴን ጭምር ሲተቹ፣ የሚደግፉት ደግሞ ወቅታዊ እርምጃ ነው ይላሉ።
እንግሊዝኛን ከቢቢሲ ይማሩ
ማጠቃለያ፡ደረጃዎ የትም ጋር ቢሆን በየሳምንቱ አዳዲስ ክፍሎችን ለማግኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ።
በአፍሪካ ቀንድ የጦር ሠፈራቸውን የመሠረቱ ኃያላን አገራት
ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ጂቡቲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያን አንዳንድ ጊዜም ኬንያን የሚያካትተው የአፍሪካ ቀንድ የዓለማችችንን ወሳኝ የባሕር ንግድ መስመርን ይዟል። በርካታ አገራትም በአካባቢው ወታደራዊ ሚና እንዲኖራቸው ይፈልጋሉ። አንዳንዶችም በቀጠናው የጦር ሠፈሮችን አቋቁመው ሠራዊታቸውን አስፍረዋል። አስካሁን ባለው ሁኔታ በአካባቢው ቁልፍ ቦታ ላይ የምትገኘው ጂቡቲ በርካታ አገራትን እያስተናገደች ነው። ሌሎቹስ?
በዩኬ ለልጃቸው የውሸት አባት ለመግዛት ከፍተኛ ገንዘብ የሚከፍሉት ስደተኛ ነፍሰጡሮች
በርካታ በዩናይትድ ኪንግደም (ዩኬ) ጥገኝነት ጠያቂ ነፍሰ ጡሮች ለሚለወደው ልጅ የውሸት አባት በመግዛት ቪዛ ለማግኘት እንደሚሞክሩ በቢቢሲ ኒውስናይት የተሠራ የምርመራ ዘገባ አጋለጠ። ድርጊቱ በምን ያህል ጥገኛ ጠያቂዎች የተፈጸመ እንደሆነ ለጊዜው መረጃ ባይኖርም፣ በርካታ ሴቶች በዚህ ዘዴ በዩኬ የመቆያ ቪዛ እንዳገኙ አመላካች ነው ተብሏል። ነፍሰ ጡር እናቶች ለዚህ የውሸት አባት በአማካይ እስከ 10 ሺህ የዩናይትድ ኪንግደም ፓውንድ እንደሚከፍሉ ቢቢሲ ማረጋገጥ ችሏል።