የላውሮ ግምት፡ ማንቸስተር ዩናይትድ በአዲሱ አሰልጣኝ ስር ውጤታማ ይሆናል?

የፎቶው ባለመብት, Reuters
ማንቸስተር ዩናትዶች በጊዜያዊው አሰልጣኝ ኦሌ ጉናር ሶልሻር ሥር የመጀመሪያ ጨዋታቸውን ለማድረግ ወደ ካርዲፍ ያቀናሉ። ምን ዓይነት ውጤት ያስመዘግባሉ?
የቢቢሲው የእግር ኳስ ተንታኝ ማርክ ላውረንሰን "ከዚህ ቀደም ከነበረው ማንቸስተር በእጅጉ የተለየ ቡድን የምንመለከት ይሆናል። በጆዜ ሞውሪንሆ ስር ውጤታማ ያልነበሩት ተጫዋቾች ትኩረት ስለሚደረግባቸው ያላቸውን ብቃት ለማሳየት ይጫወታሉ" ብሏል።
"አንድ ሁለቱ ራሳቸውን በመመልከት ውጤታማ ካልሆኑበት ውድድር ዓመት በተቃራኒ መጫወት አለባቸው።"
ላውሮ ይህንን ጨምሮ የሌሎች የፕሪሚየር ሊጉን ጨዋታዎች ግምት አስቀምጧል።
የላውሮ ግምቶች
አርብ
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ዎልቭስ ከሊቨርፑል
ከስድስት ጨዋታዎች በኋላ ሦስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ያሸነፉት ዎልቭሶች ይህን የድል ጉዞዋቸውን በዚህ ሳምንት የሚቀጥሉ አይመስለኝም።
የርገን ክሎፕ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ቡድናቸውን ቢቀያይሩም ውጤታማ ከመሆን አላገዳቸውም።
የላውሮ ግምት: 1-2
ቅዳሜ
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
አርሴናል ከበርንሌይ
አርሴናል በሊጉ በሳውዛሃምፕተን ከደረሰበት ሽንፈት በኋላ አሰልጣኝ ኡናይ ኤምሬ ማሸነፍን ብቻ አስበው ነው የሚጫወቱት።
ካርሌቶች ካለፈው ሳምንት ሽንፈት በኋላ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ገብተዋል።
የላውሮ ግምት: 2-0
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
በርንማውዝ ከብራይተን
በርንማውዞች መጥፎ ጨዋታ ባያሳዩም ካለፉት ስምንት ጨዋታዎች በሳባቱ ሽንፈት አስተናግደዋል።
ብራይተንን ግን እንደሚያሸንፉ እገምታለሁ። በተለይ ደግሞ ብራይተኖች ከሜዳቸው ውጭ ውጤታማ አለመሆናቸው ጨዋታውን ከባድ ያደርግባቸዋል።
የላውሮ ግምት: 2-0
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ቼልሲ ከሌስተር
ሌስተሮች አጥቂያቸው ቫርዲ ሲጫወት ጠንካራ ቢሆኑም በዚህ ጨዋታ ከጉዳቱ አገግሞ ቢሰለፍም ለውጥ ያመጣል ብዬ አላስብም።
ቼልሲዎች ከዎልቭስ ሽንፈት በኋላ በውጤታማነት መቀጠላቸውን የሚያረጋግጡበት ጨዋታ ነው።
የላውሮ ግምት: 2-0
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ሃደርስፊልድ ከሳውዝሃምፕተን
ሁለቱ ቡድኖች የተቀራራበ ውጤት ቢኖራቸውም ሃደርስፊልዶች ያለፉትን አራት ጨዋታዎች ተሸንፈዋል።
ጨዋታውን ያሸንፋሉ ብዬ ባልጠብቅም በአቻ ውጤት ግን ያጠናቅቃሉ።
የላውሮ ግምት: 1-1
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ማንቸስትር ሲቲ ከክሪስታል ፓላስ
ክሪስታል ፓላሶች በጣም አስፈላጊ የሆነ ድል ባለፈው ሳምንት ሌስተር ላይ ቢያስመዘግቡም ይህንን ግን ኤቲሃድ ስታዲየም ላይ ይደግሙታል ብዬ አላስብም።
ፔፕ ጉዋርዲዮላ ተጫዋቾችን ቢያሳርፍ እንኳን አጨዋወታቸው አይቀየርም። ጥሩው ዜና ደግሞ ኬቪን ደ ብሩይን እና ሰርጂዮ አጉዌሮ ከጉዳት መመለሳቸው ነው።
የላውሮ ግምት: 3-0
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ኒውካስል ከፉልሃም
ፉልሃሞች ባለፈው ሳምንት ከዌስት ሃም ጋር የነበራቸውን ዕድል ካለመጠቀማቸውም በላይ ተሸንፈዋል።
ኒውካስሎች አሁንም የመውረድ ስጋት ያለባቸው እና በሜዳቸው ውጤት ለማስመዝገብ የሚቸገሩ ቢሆንም ጨዋታውን እንደሚያሸንፉ እገምታለሁ።
የላውሮ ግምት: 2-0
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ዌስት ሃም ከዋትፎርድ
ዌስት ሃሞች ጥሩ በመንቀሳቀስ አራት ጨዋታዎችን ማሸነፍ ችለዋል። ውድድሩ ሲጀምር ችግር የነበረበት የተከላካይ መስመራቸው አሁን ቅርጽ የያዘ ይመስላል።
ይህን ጨዋታ መገመት ከባድ ነው። ባለፉት ሁለት ሳምንታት በዋትፎርዶች አጨዋወት ተደምምያለሁ።
የላውሮ ግምት: 0-2
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ካርዲፍ ከማንቸስተር ዩናይትድ
ካርዲፎች በሜዳቸው ካደረጓቸው አምስት ጨዋታዎች አራቱን በድል ቢያጠናቅቁም ይኼኛው ግን የተለየ ነው።
አዲስ አሰልጣኝ ሲመጣ ሁሉም ጠጫዋቾች ያላቸውን አቅም ማሳት ይፈልጋሉ። የኦሌ ጉናር ሶልሻር ይህን ጨዋታ በቀላሉ የሚያሸንፍ ሲሆን ቡድኑ ቀጣይ እርምጃ በጉጉት የሚጠበቅ ነው።
የላውሮ ግምት: 0-2
እሑድ
የፎቶው ባለመብት, BBC Sport
ኤቨርተን ከቶተንሃም
የቶተንሃሙ አሰልጣኝ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ በክረምት የማንቸስትር ዩናትድ አሰልጣኝ እንደሚሆኑ መነገር መጀመሩ ቡድኑ ላይ ተጽዕኖ ሊፈጥር ይችላል።
ባለፉት ጥቂት ጊዜያት ቶተንሃሞች ጉዲሰን ፖርክ ላይ ጥሩ ውጤት ነበራቸው። ባለፉት አምስት ጨዋታዎች አልተሸነፉም። ዘንድሮ ኤቨርተኖችም በሜዳቸው ውጤታማ ሲሆኑ በጨዋታው የሚሸነፉ አይመስለኝም።
የላውሮ ግምት: 1-1
• የዩናይትድ ቀጣይ ቋሚ አሰልጣኝ ማን ይሆን?
ሞሪኒሆን የሚተካው የዩናትዶች ቋሚ አሰልጣኝ ማን ይሆን? ፖቼቲኖ? ዚዳን? ወይስ ሲሞኔ?